October 21, 2021

MCPS በአትሌቲክስ ዝግጅቶች ላይ ደህንነትን ማሳደግ

ውድ የ MCPS ማህበረሰብ፦

በ MCPS የሚገኙ የአትሌቲክስ ፕሮግራሞች ለተማሪዎቻችን የአካዳሚክ ልምድን ለመደገፍ እና ለማሳደግ እንዲሁም የትምህርት ቤት እና የማህበረሰብን መልካም መንፈስ ለመገንባት የተነደፉ ናቸው። በየሳምንቱ ተማሪዎቻችን በመቶዎች በሚቆጠሩ የአትሌቲክስ ውድድሮች ውስጥ ይሳተፋሉ፣ እናም እኛ የምንጠብቀውን አክብሮት እና ስፖርታዊ ጨዋነት ሁልጊዜ ያሳያሉ። በቅርቡ በአንዳንድ ውድድሮቻችን ላይ አክብሮት የጎደለው ባህሪ አለመግባባቶች እና ክስተቶች መፈጸማቸውን የሚገልጹ ሪፖርቶች አሉ። እነዚህ ክስተቶች ጥቂት ተማሪዎችን የሚያካትቱ ቢሆኑም ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የላቸውም። በመሆኑም የተማሪዎች፣ የሰራተኞች እና የማህበረሰብ አባላት ደህንነትን ለማረጋገጥ አንዳንድ ለውጦችን እንድናጤን ያስገድዱናል፣ በተለይም ብዙ ሕዝብ በሚጠበቅባቸው ዝግጅቶች ላይ እነዚህ ለውጦች የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፡

  • የፖሊስ መኮንኖች እንዲገኙ ማድረግ፣
  • የ MCPS የደህንነት ሠራተኞችን፣ እንዲሁም የትምህርት ቤት እና የዋና ጽሕፈት ቤት የአስተዳደር ሠራተኞችን ቁጥር መጨመር፣
  • አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ መብራቶችን መጨመር፣
  • የተሳታፊዎችን ቁጥር መገደብ፣ ሁነቶችን ወደ ቅዳሜና እሁድ ቀናት ማቀድ እና/ወይም የሁነት መጀመሪያ ጊዜዎችን መለወጥ፣
  • ተማሪዎች ለመሣተፍ ሲመጡ መታወቂያዎችን እንዲያሳዩ ማድረግ እና የአንደኛ ደረጃ እና የመካከለኛ ደረጃ ተማሪዎች ከወላጅ ወይም ከአሳዳጊ ጋር እንዲሆኑ ማድረግ፤ እና
  • ሊዘጋ እንደሚችል ማስጠንቀቂያ መስጠት።

የ MCPS እና የካውንቲ አመራር አስፈላጊውን የደህንነት እርምጃዎች ለመወሰን እያንዳንዱን ክስተት እየተገመገመ በየትምህርት ቤቶቹ ይነገራቸዋል። እነዚህ እርምጃዎች በአትሌቲክስ ዝግጅቶች ላይ ማንኛውንም የወደፊት ችግሮች ለማስወገድ ይረዳሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ለማስታወስ ያህል፦ ተማሪዎች የአትሌቲክስ ውድድሮችን ጨምሮ በትምህርት ቤት ዝግጅቶች ደካማ ወይም ደህንነቱ ያልተጠበቀ ባህሪ ምክንያት የዲስፕሊን ቅጣት ሊገጥማቸው ይችላል።
የ MCPS አትሌቲክስ R.A.I.S.E. ዋና እሴቶች የአክብሮት እና ስፖርታዊ ጨዋነት፣ የአካዳሚክ ልህቀት እና የታማኝነት ባህሪን መንፈስ የተሞላ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ውድድርን፣ ፍትሃዊነትን እና ተደራሽነትን ያስተምራሉ እንዲሁም ያጠናክራሉ። በ MCPS ትምህርት ቤቶች ዝግጅቶችን ከሚከታተሉ ተማሪዎች እና ጎልማሶች ተገቢውን ባህሪ መቅረፅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው። በትምህርት ቤት ላሉት ተማሪዎቻችን ይህንን መልእክት እናጠናክራለን እና በማንኛውም የ MCPS ዝግጅት ላይ ከመገኘታቸው በፊት ልጆችዎ እነዚህን እሳቤዎች እንዲያስታውሱ እንጠይቃለን።

የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ

 



Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org

Montgomery County Public Schools