International Student Admissions

ቋንቋ ምረጡ፡-

ትምህርት ቤት መመዝገብ

 
 

አብዛኛውን ጊዜ፣ ወላጆች የአካባቢ/ቀበሌ ት/ቤት በማናገር ልጆቻቸውን ያስመዘግባሉ። ነገር ግን በአለፉት ሁለት አመታት ልጅዎ በዩናይትድ ስቴትስ ት/ቤት ካልተከታተለ/ች፣ እርስዎ በመጀመሪያ ወደ ተብሎ ወደ የሚታወቀዉ International Admissions and Enrollment/የት/ቤት ካውንስሊንግ (አማካሪ)፣ ሬዝደንሲ እና አለምአቀፍ ቅበላ ጽ/ቤት መሄድ አለብዎት።

ምንም እንኳ እርስዎ መጀመሪያ ወደ SCRIA፣ ወይም ቀጥታ ወደ አጎራባች (በቅርብዎ ወደሚገኝ) ት/ቤት ቢሄዱም፣ የተወሰኑ ሰነዶች መፈለጋቸው አይቀርም።

በSCRIA በሚኖርዎ የቀጠሮ ጊዜ፣ ሰነዶች ይታያሉ እንዲሁም የአቅራቢያ ት/ቤት ይወሰናል። የተማሪው/ዋ የትምህርት መረጃ/መዝገብ ከተገመገመ በኋላ የክፍል እና የትምህርት አይነት ምደባ አስተያየት ይቀርባል።

ከዛ በኋላ፣ ወላጅ እና ልጅ በዛው ህንጻ ውስጥ የሚገኘውን የካውንቲውን የጤና ክሊኒክ ይጎበኛሉ።    የጤና መዝገቦች ይታያሉ፣ ክትባቶች ሊሰጡ ይችላሉ፣ እንደዚሁም የክትባት የምስክር ወረቀት ይሰጣል።

በመጨረሻ  ከአስፈለገ ለአንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታ ግምገማ (English Proficiency Assessment) በESOL Testing and Accountability Center ቀጠሮ ይያዛል።

በSCRIA ከጨረሱ በኋላ፣ ከልጅዎ ት/ቤት ሬጅስትራር ጋር ተገናኝተው የምዝገባውን ሂደት መጨረስ ይኖርበዎታል። የሚከተለውን ቪዲዮ ተመልከቱ፣ መጀመሪያ ከአካባቢዎ ት/ቤት ጋር ይገናኙ

ማስታወሻ፡- ለስደተኞች እና መኖሪያ ቤት ለሌላቸው ልጆች መመሪያው/አካሄዱ ትንሽ ይለያል። ስደተኞች ወደ SCRIA ሲመጡ ይዘውት አንዲመጡ የሚያስፈልግ የተለየ የመኖሪያ ቅጽ አለ። መኖሪያ ቤት የሌላቸው ቤተሰቦች SCRIAን ወይም የአካባቢ ት/ቤትን ለመጎብኘት ቀጠሮ ከማስያዛቸው በፊት የመኖሪያ ቤት ለሌላቸው ጉዳይ አስፈጻሚ ጽ/ቤትን (Homeless Liaison Office) ማግኘት ይኖርባቸዋል።

ተዛማጅ ተያያዦች

ተጨማሪ መረጃ

በመጀመሪያ ከት/ቤትዎ ጋር ይገናኙ

ልጅዎ በዩናይትድ ስቴትስ ትምህርቱን/ቷን ሲከታተል/ስትከታተል ከቆየ/ች፣ ወይም የአለም አቀፍ ቅበላ ጽ/ቤትን ጎብኝተው ከነበረ፣ የሚቀጥለው እርምጃ የአካባቢዎን ት/ቤት ማግኘት እና የምዝባ ቀጠሮ ሬጅስትራር ተብሎ ከሚጠራው ሰው ጋር መያዝ ነው። ይህ ውይይት ቢያንስ አንድ ሰአት ሊፈጅ አንደሚችል መገመት ይችላሉ። እንግሊዘኛ በደንብ የማይናገሩ ከሆነ፣ በመጀመሪያ ት/ቤቱን ሲያናግሩ ለሠራተኛው/ዋ የቋንቋ አስተርጓሚ እንደሚፈልጉ ይንገሩ።

በስብሰባው ጊዜ፣ ተማሪው/ዋ፣ ወላጆች እና፣ ሬጅስተራሩ/ሯ ሰነዶችን ያያሉ/ይመረምራሉ፣ ስለቀደመውና ስለአዲሱ ት/ቤቶች ይነጋገራሉ፣ የምደባ ፈተናዎችን (placement tests) ያቅዳሉ፣ የት/ቤት መመሪያዎችንና ክፍያዎችን ያያሉ፣ የመጓጓዥያ አማራጮችን ይመለከታሉ እንዲሁም፣ የምግብ አካውንት ይከፍታሉ።

ወላጆች ወደ ት/ቤት ስብሰባዎች ይዘዋቸው መምጣት የሚገባቸው በርካታ ጠቃሚ ሰነዶች አሉ።
እነርሱም የሚያጠቃልሉት፡-

  • የአዲስ ተማሪ መረጃ ሰነድ
  • የተማሪው/ዋ የእድሜና፣ እርሱ ወይም እርስዋ ልጅዎ እንደሆነ/ች ማረጋገጫዎች
  • በMontgomery County ነዋሪነት ወይም፣ ስደተኛ ለመሆንዎት ማረጋገጫ
  • የሜዲካል ክትባት ማረጋገጫ፤ እና ከባለፈው ት/ቤት ማንኛውንም የትምህርት መዝገቦች

ስለ እያንዳንዱ እነዚህ ሰነዶች ዝርዝር በምዝገባ (Enrollment) ድረ-ገፅ ይገኛል።

ተዛማጅ ተያያዦች

ተጨማሪ መረጃ

የትምህርት ቤት አውቶብስን በመጓጓዣነት መጠቀም

የትምህርት ቤት አውቶብስ ግልጋሎት ነፃ ነው፣ ነገር ግን ከትምህርት ቤቱ ቢያንስ የተወሰነ እርቀት መኖር ይኖርበዎታል። የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች አንድ ማይል ወይም ከዚያ በላይ እርቀት መኖር አለባቸው። የመካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የሚሄዱ አንድ ከግማሽ ማይል፣ እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሚሄዱ ከሁለት ማይል በላይ ከት/ቤት የራቁ መሆን አለባቸው። ተማሪዎች በእግር ለመጓዝ አደገኛ ሁኔታዎች የሚገጥማቸው ከሆነ በልዩ ሁኔታ ይታያል።

በመጀመሪያ በት/ቤት ምዝገባ ጊዜ፣ ሬጅስተራሩ/ሯ የት/ቤት አውቶብስ መረጃን ከአንተ/ችና ከወላጅ ጋር ያያል/ታያለች። እያንዳንዱ የትምህርት ቤት አውቶብስ የሚጓዝበትን መስመር መመልከት ትችላለህ/ያለሽ፣ እናም የአንተ/ቺን አውቶብስ መስመር ቁጥርን ጻፈው/ጻፊው። ይህን ቁጥር መዝግበህ/ሽ ያዘው/ያዢው፣ ምክንያቱም በጣም አስፈላጊ ነው።

የአውቶብስ ከየት እንደሚወስድህ/ሽና እንደሚጥልህ/ሽ እና፣ በስንት ስዓት በአውቶብስ መቆሚያው ላይ መገኘት እንዳለብህ/ሽ ለመወሰን የአውተብስ መስመር ቁጥርን ማወቅ ያስፈልግሃል/ሻል። በአውቶብስህ/ሽ ላይ፣ ይሄ ባለአራት አሀዝ የመስመር ቁጥር በጥቁርና ነጭ ምልክት በአውቶብሱ የጎን መስኮት፣ ከመግቢያው አጠገብ ይገኛል። ተጠንቀቅ/ቂ! በአውቶብሱ ላይ የተቀባው ቁጥር አይደለም። ይልቅስ በአውቶብሱ መስኮት ላይ በጥቁር እና ነጭ ምልክት ያለው ነው።

ሁሉም ተማሪዎች በአውቶብስ በሚጓዙበት ጊዜ መመሪያዎችን እንዲከተሉ ይጠበቃሉ።

ልጅዎ የበለጠ ምቾት እንዲሰማው/ት ት/ቤትዎ ምን አልባት የገለጻ ወይም “የጓድ” ፕሮግራም ሊኖረው ይችላል - ሬጅስትራሩን ይጠይቁ። እናም ልጅዎ ከአውቶብሱ የት ቦታ መውረድ አንዳለበት/እንዳለባት እርግጠኛ ካልሆነ/ች ከአውቶብስ ሹፌሩ ቀረብ ብሎ/ላ ይቀመጥ/ትቀመጥ። ሹፌሩም በአውቶብሱ ውስጥ የሚፈጠሩ ማንኛውም ሌሎች ችግሮችን ሊፈታቸው ይችላል። እና በማንኛውም ጊዜ የእርስዎን መምህር፣ የትምህርት ቤት አማካሪ ወይም የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ስለ ስጋቶችዎ ማናገር ይችላሉ።

ብዙ ት/ቤቶች በእያንዳንዱ ሳምንት ብዙ ቀናት ከትምህርት በኋላ ለሚካሄዱ "የተግባር/እንቅስቃሴ"/አክቲቪቲ አውቶብሶችን ያንቀሳቅሳሉ። የእንቅስቃሴ/አክቲቪቲ አውተብሱ ምን አልባት እቤትህ/ሽ አቅራቢያ ሊወስድህ/ሽ ይችላል፣ ነገር ግን በትክክል ወደ ሁል ጊዜ የአውቶብስ ማቆሚያ አይሆንም። የቤትህን/ሽን አድራሻ ማስታወስ እና የእንቅስቃሴ/አክቲቪቲ አውቶብሱ የሚቆምበትን ቦታ ማወቁን እርግጠኛ ሁን/ኚ። ከዚያ ቦታ ቤት ለመድረስ እገዛ የሚያስፈልግህ/ሽ መስሎ ከተሰማህ/ሽ ለወላጅ ተናገር/ሪ።

ጓደኛ በት/ቤትህ/ሽ አውቶብስ ማምጣት ከፈለክ/ሽ፣ ያ/ች ጓደኛ የአንተን/ችን አውቶብስ  በመደበኛነት የማትጠቀም ከሆነ፣ እርሱ/ሷ የአንተን አውቶብስ መጠቀም እንደሚችል/ትችል የሚገልጽ ማስታወሻ ከወላጁ/ጇ ያስፈልገዋል/ጋታል። በአንተ/ቺ ህንጻ ትክክለኛ አሰራሩን ለማወቅ የትምህርት ቤትህን/ሽን ዋና ጽ/ቤት ተገናኝ/ኚ።

ተዛማጅ ተያያዦች

ተጨማሪ መረጃ

ምግብ በትምህርት ቤት

 

የMCPS ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ቁርስ እና ምሳ ይሰጣሉ። ተማሪዎች ከት/ቤት ካፍተሪያ ምግቦችን መግዛት፣ ወይም ምግብ ወደ ት/ቤት ይዘው መምጣት ይችላሉ።

ት/ቤት በመጀመሪያ ሲመዘገቡ ተማሪዎች አካውንት ይፈጥራሉ። ይህ አካውንት የግል መለያ ቁጥር (PIN) አለው። ምግብ ሲገዛ፣ ተማሪው/ዋ PINኑን በመጻፊያ ላይ ማስገባት ወይም የት/ቤቱ/ቷን ባለፎቶ መታወቂያ ስካን ማድረግ/ እንዲታይ ማሳለፍ ይኖርበታል/ባታል። ያ የማንኛዉንም የምግብ አይነት ዋጋ በአካውንታቸው ውስጥ ከሚገኘው ገንዘብ እንዲቀነስ ያስችላል።

ወደ አካውንቱ ገቢ ገንዘብ በተማሪዎች ሊደረግ ይችላል፣ በጥሬ ገንዘብ ወይም ቼክ። ወይም፣ ወላጆች የኦን ላይን ዘዴ ሊጠቀሙ ይችላሉ

ለልጅዎ ምግብ ለመግዛት የማይችሉ ከሆነ፣ ወላጆች ልጆቻቸው ምሳ እና ቁርስ በነፃ ወይም፣ በዝቅተኛ ዋጋ እንዲያገኙ ለሚያስችል ፕሮግራም ማመልከት ይችላሉ። ለፕሮግራሙ ብቁ መሆን የሚቻለው በቤተሰብ አባላት ቁጥር እና ገቢ መሰረት ነው። ማመልከቻው ልጅዎን መጀመሪያ በት/ቤት በሚያስመዘግቡበት ጊዜ ይሰጠወታል።

የእርስዎ ተሳትፎ በሚስጢር ይያዛል። ማን በፕሮግራሙ ውስጥ እንዳለ ወላጆች፣ አሳዳጊዎች እና የካፍተሪያ ስራ አስኪያጆች ብቻ ያውቃሉ - የልጅዎ አስተማሪ እንኳን አያውቅም/አታውቅም። በካፍተሪያ የሚገኙት የገንዘብ መቀቢያዎች ተማሪዎችን በPIN ቁጥራቸው እንዲለዩቸው ፕሮግራም የተደረጉ ስለሆነ ልጅዎ መሳተፉን ሌሎች ተማሪዎች አያውቁም።

ልጅዎ ምግብ ወደ ቤቱ/ቷ ይዞ/ዛ መምጣት ቢፈልግ/ብትፈልግ ችግር የለውም። የመካከለኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ምግባቸውን በተቆላፊ ማቆያቸው ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል። የት/ቤት ሰራተኞች ምግብ ለማብሰል፣ ማይከሮ ዌቭ ውስጥ ለማሞቅ፣ የሞቀ ውሃ ለመስጠት ወይም፣ የምግብ ነገሮችን እንዲቀዘቅዙ ለማስቀመጥ ሀላፊነት የለባቸውም።

ልጅዎ አለርጂ ወይም ልዩ የምግብ ፍላጎት ከአለው/ላት፣ ከካፍተሪያው ስራ አስኪያጅና ከት/ቤቱ ነርስ ጋር መነጋገር ያስፈልገዎታል። የጤንነት ሁኔታን የሚመለከት ጉዳይ ካለ ከትምህርት ቤቱ ነርስ ልታገኝ/ኚው የምትችለውን/የምትችይውን ቅጽ ዶክተር ሊሞላው ያስፈልጋል።

በመመገቢያ ወቅት ብዙ ተማሪዎች ከጓደኞቻቸው ጋር መብላት እና መዝናናት ይወዳሉ። አንዳንድ ጊዜ አዲስ ተማሪዎች በመጠኑ የሚያፍሩ እና ከቡድን ጋር መቀመጥን በተመለከተ እርግጠኛ አይደሉም። ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በከፋተሪያ ውስጥ ሲመገቡ የበለጠ ምቾት እንዲሰማቸው እንዲረዳቸው ት/ቤታቸው የ“ጓድ” (“buddy”) ፕሮግራም እንዳለው መጠየቅ አለባቸው።

እባክዎን ልጅዎን እርሱ ወይም እርሷ መራብ እንደማይኖርበት/ባት ስለመንገርዎ እርግጠኛ ይሁኑ። የምግብ ቤቱ ስራ አስኪያጂ፣ የምክር ባለሙያ (ካውንስለር)፣ ወይም የትምህርት ቤት አስተዳዳሪ ለማገዝ ይችላሉ። እንዲሁም እርስዎ ፣ ወላጅ የሆኑት፣ ድጋፍ ካስፈለገዎ የምግብ ቤቱን ስራ አስኪያጅ ወይም የትምህርት ቤቱን ርዕሰ መምህር ለግል ውይይት ይገናኙ።

ተዛማጅ ተያያዦች

ተጨማሪ መረጃ

ስነምግባር በትምህርት ቤት

በአለም አካባቢ ያሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተማሪዎች በበርካታ መንገዶች ይማራሉ፣ እናም ስነምግባር የሚቀረጸው በአካባቢው ባህል ነው። በMCPS ክፍሎች፣ ተማሪዎች በተደጋጋሚ ከአስተማሪያቸውና እርስ-በርሳቸው ይገናኛሉ/ይነጋገራሉ። ተማሪዎች እርስ-በርሳቸው እንዲሁም በክፍል ውስጥ ካሉ አዋቂዎች ለመማር በጥቂት ቡድኖች ሆነው ይሰራሉ። ይህም ተማሪዎች በፀጥታ እንዲቀመጡ ከሚጠበቅባቸው ጥቂት አገሮች በጣም የተለየ ነው።

ትምህርት ቤቶች ማህበረሰቦችም ናቸው። ተማሪዎች ለአዋቂዎች እና እርስ-በርሳቸው መከባበርን በማሳየት አዎንታዊ ስነምግባር እንዲኖራቸው ይጠበቃል።

በርካታ ትምህርት ቤቶች በአመቱ መጀመሪያ ጉባኤ በማካሄድ ስነምግባር እና ሌሎች የሚጠበቁትን በተመለከተ ይወያያሉ። ተማሪዎች ሁለት ሰነዶች ያገኛሉ፡- የMCPS የሥነምግባር ደንብ እና ለመብቶችና ለኃላፊነቶች የተማሪ መመሪያ

በMontgomery County፣ ወላጆች በልጃቸው የት/ቤት ህይወት በስፋት ይሳተፋሉ። ወላጆች ለወላጅ-መምህር ስብሰባዎች ይመጣሉ፣ በወላጅ-መምህር ማህበር ይሳተፋሉ፣ በክፍል ውስጥ የነጻ አገልግሎት ይሰጣሉ፣ በመስክ ጉዞዎች ጊዜ አስተማሪዎችን ያግዛሉ፣ እንደዚሁም በሌሎች የተማሪ ዝግጅቶች የነጻ አገልግሎት ይሰጣሉ። በማንኛውም ወቅት ቅሬታ ወይም ሀሳብ ሲኖርዎት የልጅዎን መምሀር፣ የት/ቤት ዋና ተጠሪ ወይም ሌላ ሥራ አስፈጻሚዎች ለማግኘት ነጻነት ይሰማዎ።

ተዛማጅ ተያያዦች

ተጨማሪ መረጃ

በትምህርት ቤት ተቆላፊ ማቆያዎች (ሎከሮች)

ተቆላፊ ማቆያ ጊዜያዊ የመጋዘን/ማስቀመጫ ቦታ ነው። ብዙ የመካከለኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተማሪዎች የግል ሎከር እንዲኖራቸው ይጓጓሉ - የራሳቸው ብለው የሚጠሩት ስፍራ! የመተላለፊያ ላይ ሎከር የጀርባ ቦርሳዎችን፣ ኮቶችን፣ መፃሀፍቶችን እና የት/ቤት መገልገያዎችን ለማስቀመጥ የተዘጋጀ ነው። ተማሪዎች በተጨማሪ የአካል ብቃት ትምህርት PE  ሲወስዱ የአካል ብቃት ትምህርት ሎከር ያገኛሉ።

ተቆላፊ ማቆያው የሚከፈተው ተከታታይ ቁጥሮችን በመጠቀም ነው። ይህም መዝጊያውን አስተማማኝ ያደርገዋል። ቁልፉን እንዴት መክፈት እንደሚችሉ ተማሪዎች እንዲያዩ ይደረጋሉ። ከዛ ለበርካታ ጊዜ መክፈትና መዝጋት ለመለማመድ እድል ይኖራቸዋል።

በተለመደ አጠቃቀም፣ በተማሪ ሎከር የሚገኙ እቃዎች የተጠበቁ ናቸው። ነገር ግን፣ ውስጡን ለማየት የግድ ከአስፈለገ፣ የት/ቤት ሰራተኞች ያለተማሪው ፈቃድ ሎከሮችን እንዲያዩ ይፈቀድላቸዋል። ሎከሮቹ የት/ቤቱ ናቸዉ፣ ስለሆነም ፍጹም የግል ነጻነት አያስተማምንም። 

የአካል ማጠናከርያ ትምህርት የሆኑ ስልጠናዎች የሚወስዱ ተማሪዎች የአካል እንቅስቃሴ  ልብሶች አንዲቀይሩ ያስፈልጋል። የPE ሎከሮች በPE ክፍለ ጊዜ የተማሪውን መደበኛ ልብሶች እና ሌሎች የግል ነገሮችን ይይዛሉ።

ሎከሮች ትንሽ ናቸው፣ ስለሆነም ተማሪዎች በውስጣቸው ሊያስቀምጡባቸው የሚችሏቸው ነገሮች የተወሰኑ ናቸው። ተማሪዎች እራሳቸውን ወይም ጓደኞቻውን አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል ማንኛውንም ነገር ሎከራቸው ውስጥ ማስቀመጥ የለባቸውም።

ተዛማጅ ተያያዦች

ተጨማሪ መረጃ

የቤት ሥራ

የቤት ሥራ አስተሳሰብ ከአንድ ባህል ወደሌላው ባህል ይለያያል። ለምሳሌ፣ በፊንላንድ፣ ብራዚል እና ኮስታሪካ፣ ተማሪዎች ከት/ቤት ውጭ በጣም ትንሽ ሥራ ነው የሚሰሩት። እንደዚሁም፣ በሻንጋይ፣ ሩሲያ እና ጣሊያን፣ ት/ቤቶች በእርግጥ በየቤት ሥራ ላይ ያተኩራሉ። አብዛኛዎቹ የአሜሪካ ት/ቤቶች በእነኝህ መካከል ላይ ይገኛሉ።

እዚህ ብዙ ት/ቤቶች የቤት ስራን የትምህርት ቀን ቀጣይ ክፍል አድርገው ያዩታል። ሥራዎች ተማሪዎች በክፍል ውስጥ ከሚማሩት ጋር በቀጥታ ይገናኛሉ። እነኝህ ተማሪዎች ክህሎቶችን እንዲለማመዱ፣ የተማሩት እንዲቆይ፣ እውቀትን እንዲያሳዩ፣ ወይም ለሚመጣው የትምህርት ክፍል እንዲዘጋጁ እድል ይሰጧቸዋል።

በጣም ወጣት/ልጅ ለሆኑ ተማሪዎች፣ የቤት ሥራ መስራት ትንሽ ደቂቃ ቢወስድ ነው - ተማሪዎች 5ኛ ክፍል ሲደርሱ እሰከ አንድ ስአት አካባቢ። በመካከለኛ ት/ቤት፣ የቤት ሥራው መጠን  ያድግና በእያንዳንዱ ምሽት ከአንድ እስከ ሁለት ስዓት ይደርሳል። እንዲሁም በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አንድ ተማሪ እንደሚወስደው/ምትወስደው የኮርስ አይነት የበለጠ ያድጋል።

በቤት ሥራ ልጅዎን ለማገዝ፣ እርስዎ የቤት ሥራ ጠቃሚ እንደሆነ እንደሚያስቡ መረዳቱን/ቷን ያረጋግጡ። እርስዎ ትኩረት መስጠትዎን ተማሪዎች ሲያውቁ እነርሱ የቤት ስራን በይበልጥ በቁምነገር መውሰድ ይችላሉ።

ተማሪዎች የተወሰኑ የትምህርት ቤት መገልገያዎች በቤት ሊኖራቸው ያስፈልጋል። በጽሞና እና ያለመረበሽ መስራት የሚችሉበት ቦታ ያስፈልጋቸዋል። በየእለቱ በተመሳሳይ ሰአት የቤት ስራ ቢሰራ በእርግጥ በጣም ያግዛል። የትምህርት መገልገያዎችን ለማግኘት ድጋፍ ካስፈለገዎ ት/ቤትዎን ያናግሩ።

እንዲሁም! ለልጅዎ የተሰጠውን/ጣትን ሥራ አይስሩ - ይሄ የተማሪው/ዋ ስራ ነው! እኛ ሁላችንም ልጆች በችሎታቸው የሚተማመኑ እንዲሆኑ እንፈልጋለን፣ እናም ያ የሚሆነው በአንድ ጊዜ አንድ ስራ በመስራት ነው። እንደ ወላጅ መገኘት ይኖርብዎታል፣ ነገር ግን በቤት ስራ ከሚገባው በላይ አይሳተፉ። እርስዎ ምን እንደሚጠብቁ በግልጽ ያሳውቁ፣ እናም የሚሰሩትን ስራዎች እና ማጠናቀቂያ ጊዜያቸውን በተመለከተ ይወቁ።

አንድ ተማሪ የተሰጠን ሥራ መጨረስ ካልቻለ/ች እርሱ/ዋ ጓደኞችን ማናገር፣ የቤተሰብ አባላትን ለእርዳታ መጠየቅ፣ እና በMCPS በቀረቡ መገልገያዎች ፣ እና  በተጠንቀቅ ላይ በሚገኝን የቤት ስራ የቀጥታ መስመር /Homework Hotline Live መጠቀመም ይኖርበታል/ባታል

ተዛማጅ ተያያዦች

ተጨማሪ መረጃ