2ኖቨምበር 4, 2021
ለተከበራችሁ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ማህበረሰብ፦
በትምህርት ቤቶች ከ ኖቬምበር 8/2021 ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውል የኳራንቲን ሂደቶችን የቅርብ ጊዜ መመሪያ ልንገልጽላችሁ እንፈልጋለን። የሜሪላንድ የጤና ዲፓርትመንት (MDH) እና የሜሪላንድ ስቴት የትምህርት ዲፓርትመንት (MSDE)የተሻሻለ የት/ቤት የኳራንቲን መመሪያ አስተላልፈዋል። የተወሰኑ መመዘኛዎች ከተሟሉ፣ተማሪዎች ኳራንቲን መቆየት አይኖርባቸውም፣ ወይም ለትንሽ ጊዜ ብቻ ማግለል ያስፈልግ ይሆናል። ይህ አዲስ መመሪያ የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ተማሪዎችን በኳራንቲን ማግለል እና በቨርቹወል ትምህርት መሣተፍ ያለባቸውን ተማሪዎች ቁጥር ይቀንሳል ተብሎ ይጠበቃል።
ምን አዲስ ነገር አለ፦
MDH እና MSDE፣ በተሰጠው መመሪያ መሰረት እና ከሞንትጎመሪ ካውንቲ የጤና እና ሰብአዊ አገልግሎት ዲፓርትመንት (DHHS) ጋር በመተባበር ከዚህ በኋላ ሁለት ምድቦች ይኖራሉ ኳራንቲን ማግለል አይኖርም ወይም ለአጭር ጊዜ ብቻ ተለይቶ የመቆየት ጊዜ በኮቪድ-19 ምርመራ ውጤት ፖዚቲቭ የሆነ(ች) ሰው ጋር ቅርብ ግንኙነት ያደረገ(ች) ሰው። የተቀራረበ ግንኙነት ማለት ፖዚቲቭ ከሆነ ሰው ጋር በ 24 ሰአት ውስጥ ከ 6 ጫማ በታች በሆነ ርቀት በጠቅላላ 15 ደቂቃዎች ወይም በትምህርት ክፍል ውስጥ ከ 3 ጫማ ርቀት በታች የተቀራረበ ግንኙነት ሲኖር ማለት ነው።
ያልተለወጡ ነገሮች፦
የኮቪድ-19 ምልክት ያለባቸው ሰዎች ለ10 ቀናት ኩራንቲን ተለይተው መቆየት አለባቸው፣ ለ14 ቀናት ራሳቸውን መከታተል እና ከ ኮቪድ-19 ምልክቶች ነፃ ከሆኑ ብቻ ወደ ትምህርት ቤቶች መመለስ የሚችሉት 100.4 ወይም ከዚያ በላይ ትኩሳት ከሌለባቸው፣ የጉሮሮ መቁሰል፣ ሳል፣ የመተንፈስ ችግር፣ ተቅማጥ፣ ማስታወክ እና ጣዕም ወይም ሽታ ማጣት ከሌለባቸው ብቻ ወደ ት/ቤቶች መመለስ ይችላሉ። ልክ እንደበፊቱ፣ የኳራንቲን መመሪያው የሚመለከተው ያልተከተቡ ግለሰቦችን ብቻ ነው። በዚህ የትምህርት ዓመት እንደታየው የተከተቡ ግለሰቦች ኳራንቲን ማግለል አያስፈልጋቸውም።
የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ
Montgomery County Public Schools
Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org