boy on scooter wearing mask

የተከበራችሁ የ MCPS ማህበረሰብ፦

የትምህርት ቦርድ ሜይ ሜይ 11 ስላካሄደው ስብሰባ፥ ስለ MCPS የማገገሚያ እቅድ እና ስለ ወደፊት ማወቅ ያለባችሁ አምስት አስፈላጊ ጉዳዮችን እነሆ፦

  1. MCPS ፎል ላይ በአካል ተገኝተው ለሚማሩ ተማሪዎች በሣምንት የአምስት ቀን መርሃግብር ይሰጣል። ፎል ላይ ሙሉ በሙሉ ዳግም ለመክፈት ቁርጠኛ ነን። ይህንንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ ጊዜ ደጋግመን ለማህበረሰቡ አጋርተናል። ተማሪዎች ትምህርት ቤት መከታተል እንዳለባቸው ይጠበቃልበአካልበሣምንት አምስት ቀን (ቨርቹወል አካደሚ ካልገቡ በስተቀር)። በተጨማሪም፥ ኤፕሪል 27 የሜሪላንድ ስቴት የትምህርት ቦርድ ለ 2021-2022 የትምህርት ዓመት ትምህርት ቤቶች ለ180 ቀናት በአካል ማስተማር እንዳለባቸው አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ውሳኔ ሰጥቷል
  2. ክትባቶች ህይወት ይታደጋሉ። የኮቪድ-19 ክትባት በመውሰድ እና ልጆቻችሁን (12 ዓመትና ከዚያ በላይ እድሜ ያላቸው) ለክትባቱ በማስከተብ እራሳችሁን እና የምትወዷቸውን ሰዎች ከወረርሽኙ ተከላከሉ። ሁሉም የሜሪላንድ ነዋሪዎች 16 እና ከዚያ በላይ እድሜ ያላቸው ሰዎች ለኮቪድ-19 ክትባት በሜሪላንድ ብዙ ሰዎች ክትባት ከሚወስዱባቸው ቦታዎች በአንዱ ወይም በካውንቲው በማናቸውም ክትባት በሚሰጥበት ክሊኒክ ቀጠሮ መያዝ ይችላሉ። ከ 12 ዓመት እስከ 15 ዓመት እድሜ ለሚገኙ ልጆች " Pfizer" ክትባት እንደሚፈቀድላቸው በመገመት እናንተም ልጆቻችሁን በቅድሚያ በማስመዝገብ ቀጠሮ መያዝ ትችላላችሁ። በመጨረሻ ተቀባይነት ካገኘ በኋላ የሞንትጎመሪ ካውንቲ የጤናና ሰብዓዊ አገልግሎቶች ዲፓርትመንት ቀጠሮ እንድትይዙ ኢሜይል ይልካል። ካውንቲው በዚህ የእድሜ ክልል ለሚገኙት በየክሊኒኮቹ በቀጣዮቹ በርካታ ቀናት ውስጥ ክትባት መስጠት እንደሚጀምር ይጠበቃል።
  3. የሞንትጎመሪ ካውንቲ ፐብሊክ ስኩልስ (MCPS) ለተማሪዎችና ለካውንቲው ነዋሪዎች ሁሉ (18 ዓመትና ከዚያ የሚያንስ እድሜ ላላቸው) በሠመር ወቅት ነፃ ምግብ መስጠቱን ይቀጥላል። በሠመር ወቅት በአካል ትምህርት ቤት የሚሳተፉ ተማሪዎች የጠዋት-ቁርስ፣ ምሳና ቁርስ ይሰጣቸዋል። በሠመር ወቅት ቨርቹወል ትምህርት ቤት የሚሳተፉ እና ሌሎች በካውንቲው ውስጥ የሚኖሩ ልጆች 7 ቀን በርካታ ምግብ የያዙ ሣጥኖችን ይወስዳሉ። ምግብ የያዙ ሣጥኖችን በካውንቲው ውስጥ ከምግብ መስጫ ጣቢያዎች በሙሉ መውሰድ ይችላሉ። የማህበረሰብ አጋሮች፥ የሃይማኖት ድርጅቶችን ጭምር፥ የአካባቢ መዝናኛ ዲፓርትመንቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ድርጅቶችም እንደዚሁ ለካውንቲው ልጆች እና ወጣቶች የሚሰጡ ምግቦችን ይወስዳሉ።
  4. የሞንትጐመሪ ካውንቲ የኮቪድ-19 ክትባት የወሰዱትን ህብረተሰብ በመቶኛ/ፐርሰንት ላይ ተሞርኩዞ እንደገና ከተከፈተ ወዲህ ወደ መጀመሪያው ምዕራፍ መገባደጃ ገብቷል። ኤፕሪል 27 የሞንቶጐመሪ ካውንቲ የጤና ጥበቃ ካውንስል ቦርድ የመጀመሪያውን ዙር የኮቪድ-19 ክትባት የወሰደ የሕዝብ ብዛት ቢያንስ አንድ በመቶ በሚደርስበት ጊዜ እንደገና የሚከፈትበትን ደንብ ምእራፍ ማካተቱ ይታወሳል።

    ምዕራፍ 1፦ 50 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከኮቪድ-19 ክትባት ቢያንስ አንድ ዶዝ በመቀበል በቤት ውስጥ የመሰብሰብ ገደቡን ወደ 50 ሰዎች ከፍ ማድረግና ከቤት ውጭ የመሰብሰብ ገደቡን ወደ 100 ሰዎች ከፍ ተደርጓል።

    ምዕራፍ 2፦ 60 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከኮቪድ-19 ክትባት ቢያንስ አንድ ዶዝ በመቀበል ቤት ውስጥ የመሰብሰቡ ገደብ ወደ 250 ሰዎች ከፍ እንዲል የሚያደርግ ሲሆን ከቤት ውጭ የሚደረጉ ስብሰባዎች ገደብ የላቸውም።

  5. የሠመር ፕሮግራሞች ምዝገባ ጁን 4 ይዘጋል። በወረርሽኙ ምክንያት የባከኑ የትምህርት ጊዜያትን ለማካካስ ዲስትሪክቱ የሚያደርጋቸው ጥረቶች አካል በመሆናቸው የሠመር ፕሮግራሞች አስፈላጊና ጠቃሚ ናቸው የደስታ ጊዜ ለማሳለፍእናበፕሮግራሞች ላይ ለመሳተፍ ለአንደኛና ለመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሚቀርቡት ፕሮግራሞች በሒሳብ፣ በሊተርሲ፣ በስፔሻልስ፣ በአእምሮ ማዳበር እና ተማሪዎችን ለሚቀጥለው የትምህርት ደረጃ በመዘጋጀት ላይ ያተኮሩ ናቸው። በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመመረቂያ አስፈላጊ በሆኑ በሁሉም ትምህርቶች ዙርያ ዳጋሚ ለሚወሰዱ ወይም ኦርጅናል ክሬዲት ክሬዲቶችን የማግኘት እድሎች ያሉ ሲሆን ክሬዲት የማይኖራቸው አማራጮችንም በአካባቢ ትምህርት ቤቶች መውሰድ ይችላሉ። ፕሮግራሞቹ፦

    • ያለምንም ወጪ ለሁሉም ተማሪዎች የሚሰጡ ሲሆን መጓጓዣም ይኖራል።
    • በሁሉም የአካባቢ ትምህርት ቤቶች/ክለስተሮች ይሰጣል
    • በጠቅላላ-ቨርቹወል እና በአካል አማራጮች ይኖራሉ


    እንደፕሮግራሙ ሁኔታ በአካባቢዎ ት/ቤት ParentVUE በመጠቀም ምዝገባ ይካሄዳል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ፕሮግራሞች ሰኞ ጁን 28 ይጀመራል፥ እና የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፕሮግራሞች ማክሰኞ፣ ጁላይ 6 ይጀመራል። ተጨማሪ መረጃ እዚህ ይገኛል። የእርስዎን ParentVUE አካውንይ እንዲሠራ ለማድረግ ድጋፍ ከፈለጉ፥ Community Support Hotline በስልክ ቁጥር 240-740-7020 ወይም በኢሜይል communitytechsupport@mcpsmd.org ይጠይቁ።



Email us: ASKMCPS@mcpsmd.org

Montgomery County Public Schools